Compartir
ባጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ (Bachir Yetekeche Rejim Guzo): መኢሶን በኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል ውስጥ (Me'eison Beethiopia Hizboch Tigil Wist)
Andargachew Assegid (Autor)
·
· Tapa Dura
ባጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ (Bachir Yetekeche Rejim Guzo): መኢሶን በኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል ውስጥ (Me'eison Beethiopia Hizboch Tigil Wist) - Andargachew Assegid
$ 1,334.54
$ 2,426.44
Ahorras: $ 1,091.90
Elige la lista en la que quieres agregar tu producto o crea una nueva lista
✓ Producto agregado correctamente a la lista de deseos.
Ir a Mis Listas
Origen: Estados Unidos
(Costos de importación incluídos en el precio)
Se enviará desde nuestra bodega entre el
Lunes 01 de Julio y el
Viernes 12 de Julio.
Lo recibirás en cualquier lugar de México entre 1 y 3 días hábiles luego del envío.
Reseña del libro "ባጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ (Bachir Yetekeche Rejim Guzo): መኢሶን በኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል ውስጥ (Me'eison Beethiopia Hizboch Tigil Wist)"
'ባጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ፡ መኢሶን በኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል ውስጥ' ለንባብ ከበቃ 20 ዓመታት አልፏል። የሚተርከው የዛሬ 45 ዓመት በኢትዮጵያ ስለተካሄደው የ1966 አብዮትና በሐምሌ 1960 ስለተመሰረተው የመኢሶን ሚና ነው። ይህ የፀሐይን የሕትመት ጥራት ደረጃ በተከተለ መልኩ የተሟላ የአርትኦት ሥራን፣ አዳዲስ ታሪካዊ ፎቶግራፎችን፣ እንዲሁም የደራሲውን አዲስ መግቢያና መጠቁም ያካተተ ነው።መፅሐፉ መኢሶን ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ እስከ ነሐሴ 1969 ድረስ ያለውን የመኢሶንን ታሪክና ሚና ይመለከታል። ከ1960 እስከ 1966 በአገር ውስጥና በውጭ በህቡዕ ሲታገል ቆየ። በየካቲት 1966 እንቅስቃሴ ውስጥ ተሳተፈ። በየካቲት 1967 የታወጀው የመሬት ላራሹ አዋጅ በሥራ እንዲተረጎም ታገለ። ከሚያዝያ 1968 እስከ ነሐሴ 1969 በነበሩት 15 ወራት ውስጥ ከደርጉ ጋር ጊዜያዊ ትብብርን መሥርቶ ሠራ። በነሐሴ 14፣ 1969 ከደርጉ ተለየ።መፅሐፉ ስምንት ክፍሎች ያሉት ሲሆን በየክፍሉ ሥር በምዕራፎች፣ በአርዕስትና በንዑስ-አርዕስት እየተዘረዘረ የቀረበ ነው። የመጀመሪያው ክፍል ከተማሪ እንቅስቃሴ ወደ ፖለቲካ ድርጅት መቋቋም የተደረገውን ጉዞና የመጀመሪያዎቹን የትግል ዘመናት ይዳስሳል። ሁለተኛው ክፍል የሚያተኩረው በቅድመ-አብዮት ዘመን በነበሩት የመኢሶን/ኢህአፓ ልዩነቶችና የፖለቲካ ትግሎች ላይ ሲሆን ሦስተኛው ክፍል ደግሞ በየካቲት አብዮት መፈንዳት፣ ሂደትና ክንዋኔ ላይ ይመለሳል። የደረሱትን ሁነቶችና ያስከተሏቸውን ውጤቶች በመዋዕለ-ዜና መልክ ለመከተል ይሞክራል። አራተኛው ክፍል በተለይ የሚመለከተው ከንጉሠ-ነገሥቱ መውርድ እስከ የካቲት የመሬት ይዞታ አዋጅ ድረስ የነበሩትን ጉዳዮች ነው። ዋናውም ጥረት ያንን ብዥ ያለ ዘመን ገለጥ ለማድረግ ነው። ክፍል አምስት ከመሬት ይዞታ አዋጅ እስከ መስከረም 1968 የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ድረስ የነበረውን “የአንድ እርምጃ ወደፊት፣ ሁለት እርምጃዎች ወደኋላ” ታሪክ ሲዘግብ፤ በተለይ የሚያተኩረው እየተደራረቡ ይደርሱ በነበሩት የኃይሎች አሰላለፍ ለውጦችና ትንቅንቆች ላይ ነው። ከዚህም ጋር በተያዘ ሂሳዊ/ገንቢ-ድጋፍ ስለተባለው የመኢሶን መስመር ነው።ክፍል ስድስት ወደ ብሔራዊ ዲሞክራቲክ አብዮት ፕሮግራም የተደረገውን ጉዞ ያትታል። በሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት መቋቋም ታሪክ ላይ ይመለሳል። ክፍል ሰባት ከጽ/ቤቱ መቋቋም በኋላ መኢሶን ያካሄዳቸውን ትግሎች የሚዘረዝር ነው። በአብዮቱ መግፋትና በተከታታይ በደረሱት የቅልበሳ ሙከራዎች ላይ ተመልሶ የሚተርክ ነው። ክፍል ስምንት የኢትዮጵያ አብዮት መጨንገፍ የጀመረበትን የመጀመሪያ ወቅት ይመለከታል። መኢሶን የትግል ስልት ያደረገበትን የፖለቲካ ምክንያቶች ያቀርባል። በ“ነጭ/ቀይ ሽብር” ጉዳይ ላይ ይመለሳል።
- 0% (0)
- 0% (0)
- 0% (0)
- 0% (0)
- 0% (0)
Todos los libros de nuestro catálogo son Originales.
La encuadernación de esta edición es Tapa Dura.
✓ Producto agregado correctamente al carro, Ir a Pagar.